ቤተክርስቲያን ቅድስት ናት፡፡

ቤተክርስቲያን ቅድስት ናት፡፡

ክርስቶስ በቅዱስ ደሙ መሥርቷታል፤ አንጽቷታል፤ ቀድሷታልና ቤተ ክርስቲያን ቅድስት ናት ኤፌሶን 5 ፥ 26፡፡የቤተ ክርስቲያን ቅድስና የተገኘው ቅድስና የባሕርይ ገንዘቡ ከሆነው ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ በመሆኑ ወደ እርስዋ የገቡ ርኩሳን ይቀደሳሉ እንጂ በውስጥዋ ያሉ ሰዎች በኃጢአት በክህደት ቢረክሱ እርስዋ አትረክስም፡፡ ዳሩ ግን እኔ ቅዱስ እንደሆንኩ እናንተም ቅዱሳን ሁኑ ባለው መሠረት በእርሱ ያመኑ በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር የተጠለሉ ሁሉ ቅድስናን ገንዘብ ሊያደርጉ ይገባል፡፡ቤተክርስቲያን ቅድስት (የተለየች) ናት ስንል ስለ አራት ነገሮችን ያመለክታል፡፡

አንደኛ፡ በደሙ የመሠረታት ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ነውና ቤተክርስቲያን ቅድስት ናት፡፡ 1ጴጥ 1፡15-16 ሐዋ 23፡20 ቤተክርስቲያን የክርስቶስ አካሉ ናትና ቅድስት ናት፡፡ እርሱም መሠረቷ አካሏና ጉልላቷ ስለሆነ ቅድስት ናት፡፡

ሁለተኛ፡-ቤተክርስቲያን የቅድስና ሥራ (አገልግሎት) የሚፈጸምባት የጸሎት ቤት ናትና ቅድስት (የተለየች) ናት፡፡ የተለየችው ለቅድስና ሥራ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ በቅድስት ቤተክርስቲያን የቅድስና ያልሆነ ሥራ መሥራት አይገባም፡፡

ሦስተኛ፡- ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ያመኑ የሰው ልጆች ምሥጢራትን ተካፍለው (ተጠምቀው ንስሐ ገብተው ሥጋና ደሙን ተቀብለው) ቅድስና ያገኙባታልና ቅድስት ናት፡፡ የቅድስና መገኛ ስፍራ ናትና ቅድስት ናት፡፡

አራተኛ፡- ቤተክርስቲያን ቅድስት የሆነችው የሰማያዊት ኢየሩሳሌም ምሳሌ ናትና ቅድስት ናት፡፡ ወደ ሰማያዊት መንግስት የምታደርስ በምድር ላይ ያለች የክርስቲያኖች ቤት ናትና ቅድስት ናት፡፡ በምድር ላይ ለእግዚአብሔር የተለየች ቅድስት ናት፡፡

አንዳንድ ወገኖች ብዙ ኃጢአት የሚሠሩና በደልን የሚፈፅሙ ሰዎች በቤተክርስቲያን ስላሉ ቤተክርስቲያን የምትረክስ (ቅድስናዋ የሚቀንስ) ይመስላቸዋል፡፡ እውነታው ግን እነዚህ ሰዎች በጊዜው በንስሐ ካልተለመሱ ራሳቸው ይረክሳሉ እንጂ ቤተክርስቲያን አትረክስም፡፡ የቤተክርስቲያን ቅድስናዋ ዘላለማዊና የማይለወጥ ስለሆነ አትረክስም፡፡ ሰው ቢያከብራት ራሱ ይከብራል፡፡ ባያከብራት ደግሞ ራሱ ይረክሳል፡፡ ይህም በአፍኒንና በፊንሐስ እንዲሁም በሐናና በሳጲራ እንደሆነው ነው፡፡ ሐዋ 5፡1 1ኛ ሳሙ 2፡12 ለምሳሌ በቆሻሻ ላይ የፀሐይ ብርሀን ቢወጣበት ቆሻሻው ይሸታል እንጂ የፀሐይ ብርሀኑ ምንም አይሆንም፡፡ የቤተክርስቲያን ቅድስናም ልክ እንደ ፀሐይ ብርሀን ነው፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s