እውነተኛይቱ ቤተክርስቲያን በሞሪያም ተራራ ትመሰላለች፡፡

እውነተኛይቱ ቤተክርስቲያን በሞሪያም ተራራ ትመሰላለች (ዘፍ 22፡12)፡፡

‹‹ከእነዚህም ነገሮች በኋላ እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው፥ እንዲህም አለው። አብርሃም ሆይ። አብርሃምም። እነሆ፥ አለሁ አለ። የምትወደውን አንድ ልጅህን ይስሐቅን ይዘህ ወደ ሞሪያም ምድር ሂድ፤ እኔም በምነግርህ በአንድ ተራራ ላይ በዚያ መሥዋዕት አድርገህ ሠዋው አለ።አብርሃምም በማለዳ ተነሥቶ አህያውን ጫነ፥ ሁለቱንም ሎሌዎቹንና ልጁን ይስሕቅን ከእርሱ ጋር ወሰደ፥ እንጨትንም ለመሥዋዕት ሰነጠቀ፤ ተነሥቶም እግዚአብሔር ወዳለው ቦታ ሄደ።

እግዚአብሔር ወዳለውም ቦታ ደረሱ፤ አብርሃምም በዚያ መሠዊያውን ሠራ፥ እንጨትንም ረበረበ፤ ልጁን ይስሐቅንም አስሮ በመሠዊያው በእንጨቱ ላይ አጋደመው። አብርሃምም እጁን ዘረጋ፥ ልጁንም ያርድ ዘንድ ቢላዋ አነሣ። የእግዚአብሔር መልአክም ከሰማይ ጠራና። አብርሃም አብርሃም አለው፤ እርሱም። እነሆኝ አለ። እርሱም። በብላቴናው ላይ እጅህን አትዘርጋ፥ አንዳችም አታድርግበት፤ አንድ ልጅህን ለእኔ አልከለከልህምና እግዚአብሔርን የምትፈራ እንደ ሆንህ አሁን አውቄአለሁ አለ። አብርሃምም ዓይኑን አነሣ፥ በኋላውም እነሆ አንድ በግ በዱር ውስጥ ቀንዶቹ በዕፀ ሳቤቅ ተይዞ አየ፤ አብርሃምም ሄደ በጉንም ወሰደው፥ በልጁም ፋንታ መሥዋዕት አድርጎ ሠዋው።›› ዘፍ 22፡1-14

እግዚአብሔር  አበ ብዙኀን አብርሃምን አንድ ልጅህን  ሠዋልኝ  ባለው ጊዜ የዋሁ ይስሀቅ ሊሠዋበት ያለው ያ የሞርያ ተራራ የቤተክርስቲያን ምሳሌ ነው፡፡ አብርሃም በህሊናው ይስሀቅን ቀብሮ እንጨት ፣ ቢለዋ፣ እሳት፣ ይዞ በደብረ ሞርያ ላይ ቢላውን አንሰቶ ሊሰዋው ሲል እግዚአብሔር ድምፁን አሰማው እንዲህ ብሎ “ አብርሃም አብርሃም ከብላቴናው ላይ እጅህን አንሳ ለምትወደው ልጅህ አልራራህምና አንተ እግዚአብሔርን የምትፈራ እንደሆንክ አውቃለሁ” ባለው ጊዜ ዞር ሲል በዕፀ ሣቤቅ የታሰረ ነጭ በግ አየ፡፡

ይስሐቅ የአዳምና ልጆቹ  ምሳሌ ነው፡፡ በእርሱ ፈንታ እውነተኛው በግ ታርዶ አድኖታልና፡፡ ዕፀ ሣቤቅ የእመቤታችን ምሳሌናት፡፡ ዕፀ ሣቤቅ በይስሐቅ ፈንታ የተሰዋውን ነጭ በግ አሰገኝታለች፡፡ እመቤታችንም ለአዳምና ለልጆቹ ቤዛነት የተሰዋውን ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለች፡፡ ነጭ በግ ደግሞ የክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ በይስሐቅ ፈንታ ተሰውቶ አዳምንና ልጆቹን አድኗልና፡፡

በሞሪያ ተራራው ላይ ይስሐቅ  ያይደለ በጉ እንደተሰዋ በቤተክርስቲያንም የሩቅ ብዕሲ ደም ሳይሆን መለኮት የተዋሀደው ነፍስ የተለየው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም ይፈተታል፡፡ ለዚህም ነው ይህች እውነተኛይቱ ቤተክርስቲያን በሞሪያ ተራራ የምትመሰለው፡፡

1 thought on “እውነተኛይቱ ቤተክርስቲያን በሞሪያም ተራራ ትመሰላለች፡፡

  1. የማሪያም ታሪክ እና የአብርሃም ታሪክ አይገናኝም በስነ አፈታት መሪህ ይህን ትርጉም ስናይ (Alagori) የማይገናኝ ክፍል አጣሞ ማዛመድ ነው ይህ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ልደረግ አይገባም ።

    Like

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s