እውነተኛይቱ ቤተክርስቲያን በደብተራ ኦሪት ትመሰላለች (ዘፀ 40፡1)፡፡
‹‹እግዚአብሔርም ሙሴን እንዲህ ሲል ተናገረው። ከመጀመሪያው ወር በፊተኛው ቀን የመገናኛውን ድንኳን ማደሪያ ትተክላለህ። በእርሱም ውስጥ የምስክሩን ታቦት ታኖራለህ፥ ታቦቱንም በመጋረጃ ትጋርዳለህ። ገበታውንም አግብተህ በእርሱ ላይ የሚኖረውን ዕቃ ታሰናዳለህ፤ መቅረዙንም አግብተህ ቀንዲሎቹን ትለኵሳለህ። ለዕጣንም የሚሆነውን የወርቅ መሠዊያ በምስክሩ ታቦት ፊት ታኖራለህ፥ በማደሪያውም ደጃፍ ፊት መጋረጃውን ትጋርዳለህ። ለሚቃጠል መሥዋዕት የሚሆነውንም መሠዊያ በመገናኛው ድንኳን በማደሪያው ደጅ ፊት ታኖረዋለህ።›› ዘፀ 40፡1-6
ይህች በብሉይ ኪዳን የነበረች ደብተራ ኦሪት ምሳሌነቷ በሐዲስ ኪዳን ላለችው አማናዊት የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው፡፡